Ethiopia TV +

የቀጥታ ስርጭት, ፊልሞች እና ሙዚቃ

ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : ጥልቅ ምርመራ ስለ ሙሴና መሐመድ ሕግጋት

ለሚመረምር ግን እውነት ቶሎ ይገለፃል፡፡ ፈጣሪ በሰው ልብ ያስገባውን ንፁህ ልቦና የፍጥረት ሕግጋትና ስርዓትን ተመልክቶ የሚመረምር እርሱ እውነትን ያገኝል፡፡ ሙሴ ፈቃዱንና ሕጉን ልነግራችሁ ከእግዚያብሔር ዘንድ ተልኬ መጣሁ  ይላል፡፡ ከርሱ በኋላ የመጡት በግብፅና በደብረሲና እንዲህ ተደረገ እያሉ ታሪክን፣ ተዓምራትን እየጨመሩ የሙሴን ነገር እውነት አስመሰሉት፡፡ የሙሴ መፅሃፍ ከፍጥረት ሕግ ሰርዓትና ከፈጣሪ ጥበብ ጋር አይስማማም፡፡ ከውስጡ የተሳሳተ ጥበብ ይገኛል፡፡ ለሚመረምር ግን እውነት አይመስለውም፡፡ በፈጣሪ ፈቃድና በፍጥረት ህግ የሰው ልጅ እንዳይጠፋ ልጆችን ለመውለድ ወንድና ሴት በፍትወተ ስጋ እንዲገናኙ ታዟል፡፡ ይህም ግንኙነት እግዚያብሔር ለሰው በሕገ ተፈጥሮ የሰጠው ነው፡፡ እግዚያብሔርም የእጁን ስራ አያረክስም፡፡ እግዚያብሔር ዘንድ እርኩሰት ሊገኝ አይችልም፡፡ ሙሴ ይህን ማለቱ ትክክል ነው አልልም፡፡ ፈጣሪውን ዋሾ እንዳደረገው ልቦናችን ያስረዳናል፡፡ እንደገናም የክርስቲያን ሕግ ለማስረጃዋ ተአምራቶች ተገኝተዋልና ከእግዚያብሔር ናት ይላሉ፡፡ ነገር ግን የወሲብ ስርዓት የተፈጥሮ ስርዓት እንደሆነ ምንኩስና ግን ልጆች ከመውለድ ከልክሎ የሰውን ፍጥረት አጥፍቶ የፈጣሪን ጥበብ የሚያጠፋ እነደሆነ ልቦናችን ይነግረናልና ያስረዳናል፡፡ የክርስቲያን ሕግ ምንኩስና ከወሲብ ይበልጣል ብትል ሐሰት ትናገራለችና ከእግዚያብሔር አይደለችም፡፡ የፈጣሪን ሕግ የሚያፈርስ እንዴት ከጥበብ በለጠ ? ወይስ የእግዚያብሔርን ስራ የሰው ምስክር ሊያስተካክለው ይቻለዋልን ? እንዲሁም መሐመድ የማዛችሁ ከእግዚያብሔር የተቀበልኩትን ነው ይላል፡፡ መሐመድን መቀበል የሚያስረዱ ተዓምራት ፀሐፊዎች አልጠፉምና ከሱም አመኑ፡፡ እኛ ግን የመሐመድ ትምህርት ከእግዚያብሔር ሊሆን እንደማይችል እናውቃለን፡፡ የሚወለዱ ሰዎች ወንድና ሴት ቁጥራቸው ትክክል ነው፡፡ በአንድ ሰፊ ቦታ የሚኖሩ ወንድ ሴት ብንቆጥር ለእያንዳንዱ ወንድ አንዲት ሴት ትገኛለች እንጂ ለአንድ ወንድ ስምንት ወይም አስር ሴቶች አይገኙም፡፡ የተፈጥሮ ህግም አንዱ ከአንዲት ጋር እንዲጋቡ አዟል፡፡ አንድ ወንድ አስር ሴት ቢያገባ ግን ዘጠኝ ወንዶች ሴት የሌላቸው ይቀራሉ፡፡ ይህም የፈጣሪን ስርዓትና ሕገ ተፈጥሮን የጋብቻንም ጥቅም ያጠፋል፡፡ አንድ ወንድ ብዙ ሴቶች ሊያገባ ይገባዋል ብሎ በእግዚያብሔር ስም ያስተማረ መሐመድ ግን ትክክል ነው አልልም፡፡ ከእግዚያብሔር ዘንድ አልተላከም፡፡ ጥቂት ስለጋብቻ ሕግ መረመርኩ ፡፡ የቀረውን ብመረምርም በህገ ኦሪትና በክርስትና በእስልምና ሕግ ፈጣሪ በልቦናችን ከሚገልፅልን እውነት እና እምነት አይስማማም፡፡ ብዙ አይገኝበትም አልኩ፡፡ ፈጣሪ ለሰው ልጅ ክፉና መልካም የሚለይበት ልቦና ሰጥቶታል፡፡ በብርሀን ብርሀን እናያለን እንደተባለውም የሚገባውን የማይገባውን ሊያውቅ፣ እውነትን ከሐሰት እንዲለይ ነው፡፡ ስለዚህ የልቦናችን ብርሀን እንደሚገባ በእርሱ ብናይበት ሊታይልን አይችልም፡፡ ፈጣሪያችን ይሄን ብርሃን የሰጠን በርሱ እንድንድን ነው እንጅ እንድንጠፋ አይደለም፡፡የልቦናችን ብርሀን የሚያሳየን ሁሉም ከእውነት ምንጭ ነው፡፡ ሰዎች ከሐሰት ምንጭ ነው ቢሉን ግን ሁሉን የሰራ ፈጣሪ ቅን እንደሆነ ልቦናችን ያስረዳናል፡፡ ፈጣሪ በመልካም ጥበቡ ከሴት ልጅ ማህፀን በየወሩ ደም እንዲፈስ አዟል፡፡ ሙሴና ክርስቲኖች ግን ይህን የፈጣሪ ጥበብ እርኩስ አደረጉት፡፡  እንደገና ሙሴ እንዲህ ያለችውን ሴት የተገናኛት ያረክሳል፡፡ ይህም የሙሴ ህግ የሴትን ኑሮ በሙሉና ጋብቻዋን ከባድ አድርጎታል፡፡ የመራባትንም ህግ አጥፍቷል፡፡ ልጆችንም ከማሳደግ ከልክሎ ፍቅርንም ያፈርሳል፡፡ ስለዚህ ይህ የሙሴ ሕግ ሴትን ከፈጠረ ሊሆን አይችልም፡፡ እንደገናም የሞቱትን ወንድሞቻችንን ልንቀብራቸው ተገቢ መሆኑን ልቦናችን ይነግረናል፡፡ በድኖቻቸውም በሙሴ ጥበብ ካልሆነ በስተቀር ከመሬት የተፈጠርንበት ወደመሬትም ልንገባባዘዘን በፈጣሪያችን ጥበብ እርኩሳን አይደሉም፡፡ ነገር ግን ለፍጥረት ሁሉ እንደሚገባ በትልቅ ጥበብ የሰራ እግዚያብሔር ስርዓቱን አያረክሳውም፡፡ ሰው ግን የሐሰትን ቃል እንዲያከብር ብሎ ሊያረክሰው ይፈልጋል፡፡ እንደገና ወንጌል አባት እና እናቱን ምሽቱን እና ልጁን ያልተወ ለእግዚያብሔር የተገባ አይሆንም ይላል፡፡ ይህ መተው የሰውን ፍጥረት ሁሉ ያጠፋል፡፡ እግዚያብሔር ግን ፍጥረቱን በማጥፋት አይደሰትም፡፡ አባትና እናትም በሽምግልናቸው ጊዜ እረዳት አተው እንዲሞቱ መተው ትልቅ አበሳ መሆኑን ልቦናችን ያሳየናል፡፡ እግዚያብሔርም አመፃን የሚወድ አምላክ አይደለም፡፡ ልጆችን መተው ግን ከበረሃ አራዊት ይብሳሉ፡፡ ምሽቱ ስታመነዝር የሚፈታት ሁሉ የፈጣሪን ስርዓትና የተፈጥሮን ሕግ አፍርሷል፡፡ ስለዚህም ወንጌል በዚህ ስፍራ የሚለው ከእግዚያብሔር ሊሆን አይችልም፡፡ እንደገና በእስልምና ሰው እንደ እንስሳ ሊሸጥና ሊገዛ ይገባል ይላሉ፡፡ ፈጣሪያችን እንደ ወንድሞች አስተካክሎ ከፈጠረን ከሰዎች ፈጣሪ ይህ የእስልምና ህግ ሊወጣ አይችልም፡፡ ልቦናችን ያውቃል እነሱ ግን ደካማን ሰው የሐይለኛ ሰው ንብረት አደረጉት፡፡ አዋቂው ፍጥረትንም ካላዋቂው እንስሳ ጋር አስተካክሎት ይህ ከእግዚያብሔር ዘንድ ሊወጣ ይችላልን ? እንደዚሁም እግዚያብሔር የከንቱ ነገር አያዝም፡፡ ይህን ብላ፣ ይህን አትብላ፣ ዛሬ ብላ፣ ነገ አትብላ አይልም፡፡ ለክርስቲያኖች እንደሚመስላቸውና የጾም ሕግጋት እንደሚጠብቁ ስጋን ዛሬ ብላ ነገ አትብላ አይልም፡፡ ለክርስቲያኖች እንደሚመስላቸውና የጾም ሕግጋት እንደሚጠብቁ ስጋን ዛሬ ብላ ነገ ግን አትብላ አይልም፡፡ እስላሞችንም እግዚያብሔር ለሊት ብሉ ቀን አትብሉ ብሎ ይሄንና የመሳሰሉትን አይላቸውም፡፡ የፍጥረታችንን ጤና የማያውክ ነገር ሁሉ ልንበላ እንደሰለጠንን ልቦናችን ያስተምረናል አንድ የመብል ቀን አንድ የጾም ቀን ግን ጤናን ያውካል፡፡ የጾም ህግ መብላትን ለሰው ሕይወት ከፈጠረና ልንበላቸው ከፈቀደ ፈጣሪ የወጣ አይደለም፡፡ በልተን ልናመሰግነው እንጅ በረከቱን ልናርም አይገባንም፡፡ ሕገ ፆም የስጋን ፍትወት ለመግደል የተሰራ ነው የሚሉም ቢኖሩ ፍትወተ ስጋ ወንድ ወደ ሴት ሊሳብ ሴትም ወደ ወንድ ልትሳብ የፈጣሪ ጥበብ ነውና እርሱ ፈጣሪ በሰራው በታወቀ ማጥፋት አይገባም እላለሁ፡፡ ፈጣሪያችን ይህን ፍትወት ለሰው ለእንስሳት ሁሉ በከንቱ አልሰጠም፡፡ ነገር ግን ለዚህ ዓለም ሕይወትና ለፍጥረት የተሰራለት መንገድ ሁሉ መሠረቱ ሆኖ እንዲቆይ ይህ ፍትወት ለሰው ልጅ ተሰጠ፡፡ አስፈላጊያችን ልንበላ ይገባናል፡፡ በእሁድ ቀንና 8 በበዓል ቀናት በአስፈላጊው ልክ የበላ እንዳልበደለ እንዲሁ በአርብ ቀንና ከፋሲካ በፊት ባሉት ቀናት ለክቶ የሚበላ አልበደለም፡፡ እግዚያብሔር ሰውን በሁሉ ቀንና በሁሉ ወራት ካስፈላጊ ምግብ ጋር አስተካክሎ ፈጥሮታል፡፡ አይሁድ፣ ክርስቲያንና እስላም ግን የፆምን ሕግ ባወጡ ጊዜ ይህን የእግዚያብሔር ሥራ ልብ አላሉም፡፡ እግዚያብሔር ፆምን ሰራልን እንዳንበላም ከለከለን እያሉ ይዋሻሉ፡፡ እግዚያብሔር ፈጣሪያችን ነው፡፡ ግን የምንበላውን ምግባችንን እንድንመገበው ሰጠን እንጂ እርሱን ልናርም አይደለም፡፡

ተዛማጅ ልጥፎች:

  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : ስለ ጌታየ ሀብቱ ሞትና የልጁ ታሪክ ካንድ አመት በኋላ ጌታየ ሀብቱ ሞተብንና እጅግ አዘንን፡፡ ትልቅ ለቅሶ አለቀስን እሱ ሳይሞት ጠርቶ ይኸው እኔ እሞታለሁ እግዚያብሔር ይጠብቃችሁ ይባርካችሁና አንተም ለልጆቼ አባት ሁናቸው አለኝ፡፡ አንድ በሬና አንድ በቅሎም ሰጠኝ፡፡ ለሚስቴም ሁለት ላሞች ከነልጆቿ ሰጣት፡፡ ስለነፍሴ ፀልዩ ብሎን በእግዚያብሔር ሰላም ሞተ፡፡ እርሱ በተባረከች ነፍሱ አረፈ… ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : የዘርዓ ያዕቆብ የፍፃሜ ታሪክ ልጄም አድጎ ያማረ ጎበዝ ሆነ፡፡ ሃያ ዓመትም በሆነ ጊዜ እርሱ ባለማወቅ ወደ ምንኩስና እናዳዘነበለ አወቅሁ፡፡ "ይህ ስራ ፈጣሪ ለኛ የሰራልንን ሥርዓት ያፈርሳልና አይገባም" ብየ ብዙ ተቆጣሁት፡፡ "ነገር ግን በተፈጥሯችን ስርዓት ሚስት አግብተህ ኑር" አልኩት፡፡ "እሺ ሚስት ስጠኝ" አለኝ፡፡ ላምጌ ከተባለው አገር መድሃኒት የተባለች የአርብቶ አደሮችን … ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : የዘርዓ ያዕቆብ ወደ እንፍራንዝ መግባት በ1625 ዓ/ም ሱስንዮስ ሞቶ ልጁ ፋሲለደስ ነገሰ፡፡ እርሱም በመጀመሪያ ፈረንጆቹን ወደደ፡፡ ግብፃዊያንንም አላባረራቸውም በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ሁሉ ሰላም ሆነ፡፡ የዚያን ጊዜ ከዋሻየ ወጥቼ መጀመሪያ ወደ አማራ አገሮች ሄድኩ፡፡ ኋላም ወደ በጌምድር ተመለስኩ ለሁሉም በፈረንጆች ጠላትነት በሱስንዮስ ዘመን ከተባረሩት መነኮሳት አንዱ መሰልኳቸው ፡፡ ስ… ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : በሃይማኖት ስለመጣው መቅሰፍትና የፋሲለደስ ታሪክ በ 1635 ዓ/ም በህዝብ ሃጢያት እና ፍቅረቢስነት ፍቅር ማጣት በኢትዮጵያ ሁሉ ትልቅ እረሃብ ብርቱ መቅሰፍት ሆነ፡፡ ንጉስ ሱስንዮስና የአቦነ አልፎንዝን ሃይማኖት የተቀበሉ ሃይማኖታቸውን ያልተቀበሉ ወንድሞቻቸውን መጀመሪያ ገደሉ፣ አባረሩ፡፡ የተሰደዱትም በኋላ ከጠላቶቻቸው ብዙዎቹን ገደሉና አፀፋ መለሱ፡፡ በኋላቸውም ሆነ በፊታቸው የእግዚያብሔር ፍርሀት … ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : ስለ ሕጋዊ የፈቃድ ጋብቻ ይህ መንገድ ወደ አበሳ ይስባልና ሴት የሌላቸው ወንድ ብቻውን ይኖር ዘንድ እንደማይገባው አወኩ፡፡ ለፊተኞቹ ሴት ታስፈልጋቸዋለች እንጅ ወንድ ብቻውን ይኖር ዘንድ መልካም አይደለም፣ እንደተባለው በሰሩት ወጥመዳቸው እንዳይጠመዱ ሰዎች ተፈጥሯቸውን ክደው ሊኖሩ አይገባቸውም፡፡ ጌታየ ሀብቱም የዘመኑን ክፋት ፈርቼ መሰልኩ እንጂ መነኩሴ አይደለሁም አልኩት፡፡ … ተጨማሪ ያንብቡ

ታዋቂ ልጥፎች

እኛ ተከታታይ ፊልሞችን እና በርካታ የተጨመረ ነጻ ይዘት ወይም የደንበኝነት ምዝገባን የሚያቀርብ ጣቢያ ነው, በእርግጥ በቀጥታ እና በቀጥታ ለመመልከት እና ጥራት ያላቸውን የጥራት ደረጃ ይዘት ለማቅረብ በምናደርጋቸው ጥረቶች እና በጥራት ላይ አናመክርም. የምንሰግበው ነጻ የዥረት አገልግሎት ከሚሰጠን በስተቀር, ተከታታይ ፊልሞችን እና ፊልሞችን ወደ ኮምፒውተርዎ ማውረድ ይችላሉ, ቆይተው ለማየት እንዲያደርጉዋቸው, ለምሳሌ የበይነመረብ ግንኙነት ከሌለዎት. በቀጥታ ወደ ፊልሞች ከመሄድ የተሻለ ይሆናል, ሁሌም አስር ኪሎ ግራም ለ 2 ሰዓታት ፊልም አንፈልግም ማለት ነው, ስለዚህ ጣቢያዎቻችን ለቀኝ እይታ እና ተከታታይ ፊልሞችን ያቀርባሉ, ይህም አንድ ጊዜ ጠቅ በማድረግ ይዘትዎን በጥሩ ጥራት ለመመልከት ያስችልዎታል. እንዲሁም በቴሌቪዥን ወይም በሌሎች የዥረት አገልግሎት ላይ ለሚደረግ ማንኛውም ምርመራ የተመረጠውን በይነመረብ በቀጥታ መመልከት ይመርጣል. አብዛኛዎቹ እነዚህ አገልግሎቶች የሚከፈልባቸው ወይም ጥራት የሌላቸው ናቸው. ጊዜን እና አላስፈላጊዎቹን ፍለጋዎች ለመቆጠብ, በጣም ደጋግመው ጣቢያውን እናምናለን, ስለዚህ አብዛኛዎቹ ፊልሞች እና ተከታታይ ፊልሞች ቅድመ እይታ ወደ መጀመሪያ ጣቢያችን ይሄድና ከሌሎች ጣቢያዎች በበለጠ ፍጥነት ይሻሻላሉ. ከተለቀቀው ፊልም ወይም ተከታታይ ጋር በጣቢያው ላይ በቋሚነት ለመመልከት ሁሉም ፊልሞች እና ተከታታይ ፊልም ቅድመ-ኮድ ውስጥ ይቀመጣሉ, ስለዚህ ስራዎን ለእርስዎ እየሠራን ስለሆነ በድር ላይ ትርጉሞችን መፈለግ የለብዎትም. የመስመር ላይ ፊልሞች እና ፊልሞች የእርስዎ አዲሱ ፊልም ነው.