Ethiopia TV +

የቀጥታ ስርጭት, ፊልሞች እና ሙዚቃ

ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : የዘርዓ ያዕቆብ ወደ እንፍራንዝ መግባት

በ1625 ዓ/ም ሱስንዮስ ሞቶ ልጁ ፋሲለደስ ነገሰ፡፡ እርሱም በመጀመሪያ ፈረንጆቹን ወደደ፡፡ ግብፃዊያንንም አላባረራቸውም በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ሁሉ ሰላም ሆነ፡፡ የዚያን ጊዜ ከዋሻየ ወጥቼ መጀመሪያ ወደ አማራ አገሮች ሄድኩ፡፡ ኋላም ወደ በጌምድር ተመለስኩ ለሁሉም በፈረንጆች ጠላትነት በሱስንዮስ ዘመን ከተባረሩት መነኮሳት አንዱ መሰልኳቸው ፡፡ ስለዚህም ወደዱኝና ምግብና ልብስም ሰጡኝ፡፡ በዚህ ሁኔታ ከአገር ወደ አገር ስመላለስ የካህናቶቿን ክፋት አውቃለሁና ወደ አክሱም መመለስን አልወደድኩም፡፡ ሰው የሚሄድበት ከእግዚያብሔር እንደሚታዘዝ አሰብኩ፡፡ ጌታ ሆይ የምሄድበትን መንገድና የምኖርበትን ነገር ምራኝ አልኩት፡፡ ወደጎጃም ምድር ተሻግሬም ለመኖር አሰብኩ፣ ነገር ግን እግዚያብሔር ወደአላሰብኩት መራኝ፡፡ አንድ ቀን ወደ እንፍራንዝ አገር ወደ አንድ ጌታ ሰው የእግዚያብሔር ሀብት ነውና ሀብቱ ወደ ተባለ ደረስኩ በዚያውም አንድ ቀን አደርኩ፡፡ በማግስቱም አክሱም ወዳሉት ዘመዶቼ ደብዳቤ እንድልክ ከእርሱ ቀለምና ወረቀት ለመንኩት፡፡ ይህ ሰውም "አንተ ፀሀፊ ነህ ወይ?" አለኝ "አዎ ፀሀፊ ነኝ" አልኩት "ከኔ ጋር ጥቂት ቀን ተቀምጠህ የዳዊት መዝሙርን ፃፍልኝና ዋጋህን እሰጥሀለሁ" ብሎ ተናገረኝ "እሺ" አልኩት፡፡ የድካሜንም ፍሬ የምመገብበትን መንገድ ስላሳየኝ እግዚያብሔርን በልቤ አመሰገንኩት፡፡ እውነት ባስተምር ሰዎች ሊጠሉኝና ሊከሱኝ፣ ሊያባርሩኝ ካልሆነ አይሰሙኝምና ወደ ቀድሞ ሊቅነቴ ተመልሼ ሐሰትን ማስተማር ጠላሁ፡፡ እኔ ግን ከሰው ሁሉ ጋር በፍቅርና በሰላም መኖርን ወደድኩ፡፡ በሃጥአን ቤት ከብሬ ከምኖር ግን ከሰው ተለይቼ የድካሜን ፍሬ እየተመገብኩ እግዚያብሔር በሰጠኝ ጥበብ ተሸሽጌ አልባሌ መስየ መኖርን መረጥኩ፡፡ በጥቂት ጊዜም ቀለምና ብራና አዘጋጅቼ አንድ 16 የዳዊት መዝሙር ፃፍኩ፡፡ ፅህፈቴም ያማረች ናትና ጌታዮ ሀብቱና ሁሉም አይተዋት ተደነቁ፡፡ ጌታዮ ሀብቱም ደሞዜን አንድ መልካም ልብስ ሰጠኝ ፤ ደግሞም ወልደ ሚካኤል የተባለ የጌታየ ሀብቱ ልጅ ላባቴ እንደፃፍከው ለእኔም ፃፍልኝ አለኝና ፃፍኩለት፡፡ አንድ በሬና ሁለት ፍየሎችም ሰጠኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ብዙዎች ወደ እኔ ዘንድ መጥተው ዳዊትና ሌሎች መፅሐፍትን፣ ደብዳቤዎችን አፃፉ፡፡ በዚያ አገር ካለ እኔ በቀር ሌላ ፀሐፊ አልነበረምና ልብስ፣ ፍየሎች፣ እህል፣ ጨውና ሌላም እነርሱን የመሳሰሉ ሰጡኝ፡፡ ለጌታየ ሀብቱም አንድ ወልደ ገብርኤል ተሰማ የተባለና ሁለተኛ ወልደ ህይወት ምትኩ የተባሉ ሁለት ልጆች ነበሩት፡፡ አባታቸው ሀብቱም የሚበቃህን ምግብ እሰጥሃለሁና በእጅህ ፅፈህ የምታፈራውን ላንተ ይሆናልና፤ የዳዊትን ንባብ አስተምራቸው አለኝ፡፡ አባቴ ሆይ ያዘዝከኝን ሁሉ አደርጋለሁ አልኩት፡፡ ነገር ግን ካንተ በቀር ዘመድ የለኝምና በአባቴና በእናቴ ዘመዶችም ፋንታ ዘመድ ሁነኝ አልኩት፡፡ 

ተዛማጅ ልጥፎች:

  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : ስለ ሕጋዊ የፈቃድ ጋብቻ ይህ መንገድ ወደ አበሳ ይስባልና ሴት የሌላቸው ወንድ ብቻውን ይኖር ዘንድ እንደማይገባው አወኩ፡፡ ለፊተኞቹ ሴት ታስፈልጋቸዋለች እንጅ ወንድ ብቻውን ይኖር ዘንድ መልካም አይደለም፣ እንደተባለው በሰሩት ወጥመዳቸው እንዳይጠመዱ ሰዎች ተፈጥሯቸውን ክደው ሊኖሩ አይገባቸውም፡፡ ጌታየ ሀብቱም የዘመኑን ክፋት ፈርቼ መሰልኩ እንጂ መነኩሴ አይደለሁም አልኩት፡፡ … ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : የዘርዓ ያዕቆብ የፍፃሜ ታሪክ ልጄም አድጎ ያማረ ጎበዝ ሆነ፡፡ ሃያ ዓመትም በሆነ ጊዜ እርሱ ባለማወቅ ወደ ምንኩስና እናዳዘነበለ አወቅሁ፡፡ "ይህ ስራ ፈጣሪ ለኛ የሰራልንን ሥርዓት ያፈርሳልና አይገባም" ብየ ብዙ ተቆጣሁት፡፡ "ነገር ግን በተፈጥሯችን ስርዓት ሚስት አግብተህ ኑር" አልኩት፡፡ "እሺ ሚስት ስጠኝ" አለኝ፡፡ ላምጌ ከተባለው አገር መድሃኒት የተባለች የአርብቶ አደሮችን … ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : ስለ ጌታየ ሀብቱ ሞትና የልጁ ታሪክ ካንድ አመት በኋላ ጌታየ ሀብቱ ሞተብንና እጅግ አዘንን፡፡ ትልቅ ለቅሶ አለቀስን እሱ ሳይሞት ጠርቶ ይኸው እኔ እሞታለሁ እግዚያብሔር ይጠብቃችሁ ይባርካችሁና አንተም ለልጆቼ አባት ሁናቸው አለኝ፡፡ አንድ በሬና አንድ በቅሎም ሰጠኝ፡፡ ለሚስቴም ሁለት ላሞች ከነልጆቿ ሰጣት፡፡ ስለነፍሴ ፀልዩ ብሎን በእግዚያብሔር ሰላም ሞተ፡፡ እርሱ በተባረከች ነፍሱ አረፈ… ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ መግቢያ እግዚያብሔርን የምትፈሩ ሁሉ ለነፍስ ያደረጋችሁትን መናገር እጀምራለሁና ኑ ስሙኝ፡፡ ሁሉን በፈጠረ መጀመሪያና መጨረሻ በሆነ ሁሉን በያዘና የህይወትና የጥበብ ሁሉ ምንጭ በሆነ እግዚያብሔር በሰጠኝ ረዥም እድሜየ ትንሽ እፅፋለው፡፡ ነፍሴ በእግዚያብሔር ዘንድ የተከበረች ትሁን ጆሮዎችም ሰምተው ይደሰቱ፡፡ እኔ እግዚያብሔርን ፈለኩት መለሰልኝ፡፡ አሁንም እናን… ተጨማሪ ያንብቡ
  • ሓተታ ዘርአ ያዕቆብ : በሃይማኖት ስለመጣው መቅሰፍትና የፋሲለደስ ታሪክ በ 1635 ዓ/ም በህዝብ ሃጢያት እና ፍቅረቢስነት ፍቅር ማጣት በኢትዮጵያ ሁሉ ትልቅ እረሃብ ብርቱ መቅሰፍት ሆነ፡፡ ንጉስ ሱስንዮስና የአቦነ አልፎንዝን ሃይማኖት የተቀበሉ ሃይማኖታቸውን ያልተቀበሉ ወንድሞቻቸውን መጀመሪያ ገደሉ፣ አባረሩ፡፡ የተሰደዱትም በኋላ ከጠላቶቻቸው ብዙዎቹን ገደሉና አፀፋ መለሱ፡፡ በኋላቸውም ሆነ በፊታቸው የእግዚያብሔር ፍርሀት … ተጨማሪ ያንብቡ

ታዋቂ ልጥፎች

እኛ ተከታታይ ፊልሞችን እና በርካታ የተጨመረ ነጻ ይዘት ወይም የደንበኝነት ምዝገባን የሚያቀርብ ጣቢያ ነው, በእርግጥ በቀጥታ እና በቀጥታ ለመመልከት እና ጥራት ያላቸውን የጥራት ደረጃ ይዘት ለማቅረብ በምናደርጋቸው ጥረቶች እና በጥራት ላይ አናመክርም. የምንሰግበው ነጻ የዥረት አገልግሎት ከሚሰጠን በስተቀር, ተከታታይ ፊልሞችን እና ፊልሞችን ወደ ኮምፒውተርዎ ማውረድ ይችላሉ, ቆይተው ለማየት እንዲያደርጉዋቸው, ለምሳሌ የበይነመረብ ግንኙነት ከሌለዎት. በቀጥታ ወደ ፊልሞች ከመሄድ የተሻለ ይሆናል, ሁሌም አስር ኪሎ ግራም ለ 2 ሰዓታት ፊልም አንፈልግም ማለት ነው, ስለዚህ ጣቢያዎቻችን ለቀኝ እይታ እና ተከታታይ ፊልሞችን ያቀርባሉ, ይህም አንድ ጊዜ ጠቅ በማድረግ ይዘትዎን በጥሩ ጥራት ለመመልከት ያስችልዎታል. እንዲሁም በቴሌቪዥን ወይም በሌሎች የዥረት አገልግሎት ላይ ለሚደረግ ማንኛውም ምርመራ የተመረጠውን በይነመረብ በቀጥታ መመልከት ይመርጣል. አብዛኛዎቹ እነዚህ አገልግሎቶች የሚከፈልባቸው ወይም ጥራት የሌላቸው ናቸው. ጊዜን እና አላስፈላጊዎቹን ፍለጋዎች ለመቆጠብ, በጣም ደጋግመው ጣቢያውን እናምናለን, ስለዚህ አብዛኛዎቹ ፊልሞች እና ተከታታይ ፊልሞች ቅድመ እይታ ወደ መጀመሪያ ጣቢያችን ይሄድና ከሌሎች ጣቢያዎች በበለጠ ፍጥነት ይሻሻላሉ. ከተለቀቀው ፊልም ወይም ተከታታይ ጋር በጣቢያው ላይ በቋሚነት ለመመልከት ሁሉም ፊልሞች እና ተከታታይ ፊልም ቅድመ-ኮድ ውስጥ ይቀመጣሉ, ስለዚህ ስራዎን ለእርስዎ እየሠራን ስለሆነ በድር ላይ ትርጉሞችን መፈለግ የለብዎትም. የመስመር ላይ ፊልሞች እና ፊልሞች የእርስዎ አዲሱ ፊልም ነው.